ሐሙስ 21 ዲሴምበር 2017

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ470 ሚሊየን ዶላር ብድር እና እርዳታ ሰጠ

 የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ለእንሰሳትና አሳ ሀብት ምርት ማሻሻያ የሚውል የ470 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ብድር እና እርዳታ ሰጠ።
የብድር ስምምነቱን የተፈራረሙት የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ሚንስትር ዶክተር አብርሃም ተከስተ እና የዓለም ባንክ ተወካይ ካሮሊን ተርክ ናቸው።
ከተገኘው ገንዘብ ውስጥ 300 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላሩ በትምህርት መስክ በተለይ በአርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢ ለሚኖሩ ዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ የሚደረገውን ጥረት እንዲያግዝ የሚውል ነው።
ድጋፉ ለልዩ ፍላጎት ተማሪዎች በቂ የትምህርት አቅርቦት እንዲኖር እንደሚያስችልም ተነግሯል።
በተጨማሪም በእንሰሳት እና አሳ ሀብት ሀገሪቱ ያላትን አቅም በማሳደግ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚያግዝ ታምኖበታል።
 (ኤፍ ቢ ሲ) በኤርሚያስ ፍቅሬ

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ