ረቡዕ 29 ጁን 2016

በአውሮፓ ዋንጫ 8ቱ ሀገራት ታውቀዋል፤እኛ ደግሞ ቀጣዩቹን ከምርጥም ምርጥ 4 የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች

የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች
ሀሙስ ሰኔ 23 ቀን 2008 ዓ.ም
*ፓላንድ 4፡00 ፓርቹጋል
አርብ ሰኔ 24 ቀን 2008 ዓ.ም
*ዌልስ 4፡00 ቤልጄም
ቅዳሜ ሰኔ 25 ቀን 2008 ዓ.ም
*ጀርመን 4፡00 ጣሊያን
እሁድ ሰኔ 26 ቀን 2008 ዓ.ም
*ፈረንሳይ 4፡00 አይስላንድ
source፦ኢትዮ አዲስ ስፖርት

ማክሰኞ 28 ጁን 2016

በ1ኛ እጣ 10 ሚሊየን ብር የሚያሸልመው የቶምቦላ ሎተሪ እጣ ወጣ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2008 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለታላቁ ህዳሴ ግድቡ ግንባታ የሚውለውና በ1ኛ እጣ 10 ሚሊየን ብር የሚያሸልመው የቶምቦላ ሎተሪ እጣ ወጥቷል።
ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና የከተማዋ ነዋሪዎች በተገኙበት በብሄራዊ ሎተሪ አዳራሽ በወጣው እጣ “2913750” 10 ሚሊየን ብር የሚያሸልመው የእጣ ቁጥር ሆኖ ወጥቷል።
5 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የሁለተኛ ዕጣ ቁጥር 0497398 ሲሆን፥ 2 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ አሸናፊ ቁጥርም 0207494 ሆኗል።
በተመሳሳይ 1 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የአራተኛ ዕጣ አሸናፊ ቁጥር 2707403 በመሆን በብሄራዊ ሎተሪ አዳራሽ ወጥቷል።
በእጣ አወጣጥ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሮማን ገብረሥላሴ፥ የግድቡ ግንባታ በጠንካራ ህዝባዊ ተሳትፎ ተጠናክሮ ቀቀጠሉን ተናግረዋል።
ለግድቡ ግንባታ ገቢ ማሰባሰቢያነት የተዘጋጀው ሎተሪው ከየካቲት 1 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ በገበያ ላይ መዋሉና ከሽያጩም ከ150 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱም ይታወሳል።

አንድ ለትምህርት ቤቱ አዲስ የሆነ መምህር ክላስ ዉስጥ ገብቶ እራሱን ካስተዋወቀ በኃላ ። . አንድ ተማሪ ጋሸ ስለ ጠቅላላ እዉቀት ጥያቄ አለኝ ብሎ

By
Michael Negese
አንድ ለትምህርት ቤቱ አዲስ የሆነ መምህር ክላስ ዉስጥ ገብቶ እራሱን ካስተዋወቀ
በኃላ ። .
አንድ ተማሪ ጋሸ ስለ ጠቅላላ እዉቀት ጥያቄ አለኝ ብሎ
ተነሳ።።።።።።።።።።።።።
.
ተማሪ፦ ዝሆንን ፍሪጅ ዉስጥ ለማስገባት ብንፈልግ
እንዴት አድርገን እናስገበዋለን?
.
መምህር፦አላወኩም
.
ተማሪ፦ቀላል እኮነዉ ፤ፍሪጁን በመክፈት፥ ሌላም ጥያቄ
አለኝ።
.
መምህር፦እሽ ቀጥል
.
ተማሪ፦አህያንስ ፍሪጅ ዉስጥ ማስገባት ብንፈልግስ
እንዴት አድርገን ነዉ የምናስገባት?
.
መምህር፦ይችማ ቀላል አይደለች፣ ፍሪጅን በመክፈት
.
ተማሪ፦አይደለም ፤መጀመርያ ዝሆኑን ማዉጣት
.
መምህር፦ይገርማል
.
ተማሪ፦አሁንም ጥያቄ አለኝ
.
መምህር፦እሽ
.
ተማሪ፦ሁሉም እንስሳ የነብር ልደት ሁኖ ሂደዋል አንድ
እንስሳ ብቻ ቀረ ማነዉ እሱ?
.
መምህር፦አበሳ ምክንያቱም ሁሉንም እንስሳት
ስለሚበላቸዉ።
.
ተማሪ፦አይደለም፣አህያ ነች ምክንያቱም ከሰሀታት በፊት
ፍሪጅ ዉስጥ ስለነበረች።
..
መምህር፦እየቀለድክ ነዉ?
.
ተማሪ፦አሁን የመጨረሻ ጥያቄ ባህር ተሻግረህ ለማለፍ
ፈራህ ምክንያቱም አዞ አለ
ብለህ ስለምታስብ።እንዴት ብለህ መሻገር ትችላለህ?
.
መምህር፦በጀልባ ነዋ !
.
ተማሪ፦አይደለም ፣እየዋኘህ አዞ ለ ነብር ልደት ስለሄደ ።.

የኢትዮ ጵያ ፕሪሜርሊግ የመዘደጊያ ስነስርዓት በነገው እላት ይካሄዳል።

የኢትዮ ጵያ ፕሪሜርሊግ የመዘጊያ ስነስርዓት በነገው አለት የሚካሄድ  ሲሆን አሸናፊው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራም ዋንጫ ይረከባል ከዛበፊት የሚደረጉ ጨዋታዎች
ረቡዕ ሰኔ 22 ቀን 2008 ደደቢት ከ ሀድያ ሆሳዕና 8:30 (አ/አ ስታዲየም) ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ አዋሳ ከነማ 11:30 (አ/አ ስታዲየም)

ክፍት የስራ ማስታወቂያ

የሳምንቱ ምርጥ አባባል

ሰዎች ለዘላለም እንዳይረሱህ ከፈለክ ተበደራቸውና ሙት።

በመፋቀራችን… እግዚአብሔር ቅር አይለውም ፤ አላህ አይከፋውም ፡፡

በመፋቀራችን… እግዚአብሔር ቅር አይለውም ፤ አላህ አይከፋውም ፡፡ (መላኩ አላምረው) ========== ... መግቢያ፦ ከመካ ቀጥለን ከአፍሪካ ቀድመን በክርስቲያን አምባ መስጊዱን አቁመን እስላም ክርስቲያኑ በአንድ ላይ ከትመን በዓላችሁ በዓላችን በዓላችን በዓላችሁ ደስታችሁ ደስታችን ደስያችን ደስታችሁ ሆኖ የጠበቀን ከአበው የወረስነው ኢትዮጵያዊነት ! መለያችን ይህ ነው። .... ሀተታ፦ በእውነት ከሆነ... በእኛ የጥምቀት በዓል የእናንተ መንዙማ በአረፋ በመውሊድ... ያሬዳዊ ዜማ (ለአምልኮ ሳይሆን ለፍቅር ቢሰማ) እግዚአብሔር ቅር አይለውም አላህ አይከፋም ጽድቅ በክፋት እንጅ በፍቅር አይጠፋም። … የጽድቅን አኗኗር - አዛባነው እንጅ እያበዛን ጣጣ በሰው ልጆች ዓለም - ከፍቅር የሚሻል ጽድቅ ከየት ሊመጣ ? ... ‹‹ምንም ጽድቅ ያለ-እምነት ሊታሰብ ባይችልም ያለ-ፍቅርም እምነት ቅዠት ነው ከንቱ ህልም ።›› ... እኛም በእኛ እምነት እናንተም በእናንተ መንግሥቱን ለመውረስ ልባችን ከሻተ እምነታችን "በሩ" ቢሆንም ባይሆንም መንገዳችን ገነት ከቶ አያደርሰንም ፍቅር የሌለንን ፈጣሪ አያውቀንም ። ምክንያቱም... ዘላለም ሚገዛው ዓለማትን ፈጥሮ ፈጣሪ ፍቅር ነው ! ለፍቅር የፈጠረን በፍቅር ቀምሮ ። ... ‹‹ፍቅርን ያለ ፍቅር ለማግኘት ሙከራ ይህ ከንቱ ድካም ነው የሰነፎች ሥራ ።›› ... በእኛ መጽሐፍ ቅዱስ... ‹‹ሁሉም ነገር ባንተ በፍቅር ይሆን ዘንድ አይደለም ወዳጅህን ጠላትህ ውደድ›› የሚል ትዕዛዝ አለ... ትርጉሙም ምሥጢሩም "ፍቅርን" ያከለ የፍቅርን አስገኝ "እ ር ሱ ን" የመሰለ ። በእናንተ ቁርዓንም... ‹‹እንኳንስ ለሰው ልጅ ለፍጥረቱ ሁሉ ራርታችሁ ኑሩ እደሩ እንደ ቃሉ›› ተብሎ የተጻፈ የፍቅር ቃል አለ ክርስቶሳዊውን የእኛን የመሰለ ። ... መደምደሚያ፦ ፍቅር ከሆነ አምላክ ለሰው የተሰጠ ምንም ትዕዛዝ የለም ከፍቅር የበለጠ ... እኛ ስንዋደድ ዓይኑ ደም ሚለብስ ልባችን ሲፋቀር እግሩ የሚያነክስ ሰይጣናዊ ፍጡር ከሰው ልጅ ባይጠፋም በመፋቀራችን - እግዚአብሔር ቅር አይለውም - አላህ አይከፋም፤ ጽድቅ በክፋት እንጅ በፍቅር አይጠፋም ። ……… (©መለኛ ሐሳቦች)

መልካም ልደት ለአባባ ተስፋዬ

"ደህና ናችሁ ልጆች? የዛሬ ኣበባዎች የነገ ፍሬዎች
እንደምን ኣላችሁ ልጆች? ኣያችሁ ልጆች የኢትዮጲያ
ቴሌቭዥን የልጆች ግዜ ዝግጅት ክፍል እናንተን
ለማስደሰት ልክ በሰአቱ ይገኛል፥ እናንተስ ዝግጁ ናችሁ?
ኣዎዎ ኣባባ ሸንተረሩን ኣቋርጠው ዳገቱን ወጥተው
ቁልቁለቱን ወርደው በጓሮ በኩል ዲ ዲ ዲ ከተፍ ሲሉ
እናንተ ደሞ ቆማችኋል ኣይደል? በጣም ጥሩ ነው ልጆች፥
ኣንድ ኣባት ሲመጣ ብድግ ብሎ በኣክብሮት መቀበል
ኣስፈላጊ መሆኑን ሁልጊዜ እነግራችሁ የለም? ኣዎዎ በቃ
አሁን ተቀመጡ እንዳትጋፉ ታዲያ ትንንሾች ወደፊት
ትልልቆች ወደኋላ ኣዎዎ"
ሰኔ 20/1916 ዓ.ም በቀድሞዋ ባሌ ክፍለ ሃገር ከዶ
የተሰኘ አካባቢ ኣንድ ጀግና ፈለቀባት፥ ብላቴናው 14
ዓመት ሲሞላው ወደ ሸገር መጣ ከዚያም በኮከበ ፅባህ
ኣስኳላ ትምህርቱን መከታተል ጀመረ።
በኣንድ ወቅት የኣዲስ ኣበባ መስተዳደር ባህል እና ቲያትር
ኣዳራሽ ማስታወቂያ ሲወጣ በተዋናይነት ተመዝግቦ
ተቀጠረ፥ በወቅቱ ሴት ልጅ ወደ ማጀት እንጂ ኣደባባይ
ላይ መዋል ነውር ነበርና ለትወና የምትመጣ ሴት
ኣልነበረችም እናም ይህ ሰው የሴቶችንም ገጸባህሪ
ወክሎ በብቃት ይጫወት ጀመር። እንዲያውም ኣንድ
ወቅት ላይ ኣንድ ትያትር ሊያይ የገባ ሰው "ይህቺን ሴት
ወድጃለሁ" ብሎ ኣምባጓሮ እስኪፈጠር መስሎ ሳይሆን
ሆኖ የሚተውን እሳት ተዋናይ ነበር፥ ለዚህም
- ‘ሀ ሁ በስድስት ወር’
- ‘ኤዲፐስ ንጉስ’
- ‘አሉላ አባነጋ’
- ‘ዳዊትና ኦርዮን’
- ‘ኦቴሎ’
- ‘አስቀያሚዋ ልጃገረድ’
- ‘ስነ ስቅለት’
የተሰኙ እሱ የተጫወተባቸው ተውኔቶች ዉስጥ የሚጠቀሱ
ናቸው፥ ይህ ሰው ወደ ድርሰቱ ኣለም ገብቶም
- ‘ብጥልህሳ’
- ’ ነው ለካ’
- ‘ጠላ ሻጯ’
የተሰኙ ተውኔቶች ኣበርክቶ ግዙፍ ኣሻራውን ያሳረፈ ሲሆን
በተጨማሪም አራት የተረት መጻሕፍት ለልጆች ኣድርሷል።
በ1957 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሲቋቋም ደግሞ
"የልጆች ግዜ" የተሰኝ ፕሮግራም እንዲኖር ሃሳቡን አቅርቦ
ሲፀድቅለት እስካሁንም ማንም ሊተካው ባልቻለና የእርሱ
ብቻ በሆነ የአቀራረብ መንገድ በመጠቀም ለመላው
የኢትዮጲያ ህዝብ ለ42 ዓመታት ያህል በኣባትነት ስሜት
ኣቅርቧል።
ለልጆች ብቻ ሳይሆን ለኣዋቂም የሚሆኑ ወዝ ያላቸው
ቁምነገር ኣዘል ተረቶችን፣ ጨዋታዎችን እና ኣስተማሪ
ዝግጅቶችን እያደረሰ መልካም ማንነትን የተላበሰ ትውልድ
ለመገንባት መተኪያ የሌለው ኣስተዋፅዖ እና ድርሻ
ኣበርክቶልናል።
ኣባባ ተስፋዬ እንኳን ለ93ኛ ዓመት የልደት በዓልዎ
ኣደረሰን፥ ውለታዎ ብዙ ነው ትውልዶች ሁሉ ሲያከብርዎት
ይኖራሉ እርስዎ በተለያየ ዘመን ውስጥ፥ በኣስቸጋሪውም
በጥሩውም የሀገር ሁናቴ በሚልየን ለሚቆጠሩ የኢትዮጲያ
ልጆች ስለ ሐገራቸው እንዲታስቡ መምህር የሆኑ
የትውልድ ኣባት ነዎትና እናከብርዎታለን፡፡ እንደ ትላንቱ
ሁሉ ሁሌም እርስዎን ስናስብ ከመቀመጫችን ብድግ
ብለን ልናከብርዎት የውዴታ ግዴታችን ነው። ከዛሬ ጀምሮ
የሚታሰብ ከእኔ እድሜ ተቆርጦ ለእርስዎ ለኣባቴ ቢሰጥ
እወዳለሁ
ልጅዎ

ምንጭ: Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

ዓርብ 3 ጁን 2016

#The Stone Roses could be poised to play

two secret gigs in Manchester, the M.E.N.
can reveal.
The band's management have refused to
confirm or deny reports that the band are
gearing up for a short run of hush-hush
gigs in an undisclosed city venue for a
small gathering of fans.
According to a Facebook post published
today, one person claims to have seen the
tickets, along with details of the gigs and
believes that tickets are to be released at
10am on Saturday (June 4).
The poster suggests Ian Brown and co will
play at a venue in Greater Manchester,
possibly somewhere between Manchester
and Oldham, as a warm up to their sold-
out stadium shows at the Etihad later this
month

ዳጉ፤ አስደናቂው የአፋሮች የመረጃ ልውውጥ እሴት፤=====================================

(ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ
ፍለጋው ወደ አፋር እየወሰደን ነው፡፡ የአፋርን አስደናቂ
መስህቦች ከመጎብኘታችን በፊት ስለ ዳጉ ማወቅ አለብን
ይላል፡፡ ዳጉ ካለን አፋርን እንዲህ እንጎበኘዋለን፡፡)
(ሔኖክ ስዮም በድሬትዩብ)
የአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ፍለጋችንን ከዚህ በላይ
አንገፋበትም፡፡ ወደ አፋር ምድር ጉዞአችንን ቀጥለናል፡፡
ሱልጣኑ እንደአሉት እንኳን አፋሮች ግመሎቻቸው
የአንድነታችን መገለጫዋን ባንዲራችንን ያውቋታል፡፡
ወደዚህ ምድር እየሄድን ነው፡፡
አምስት ዞን 31 ወረዳና አንድ ልዩ ወረዳ የፈጠሩት
የአፋር ክልል 96,256 ስኩዬር ኪሎ ሜትር የቆዳ ስፋትን
ይሸፍናል፡፡ በታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ
ውስጥ ያረፈው አፋር ምድር ከባህር ጠለል በታች እስከ
116 ሜትር የሰረጎዱ ሸለቆዎች የሚገኙበት ሲሆን ሙሳ
አሊ ከባህር ጠለል በላይ 2063 ሜትር የሚዘረዝመው
አፋር ትልቁ ተራራ ነው፡፡
አዋሽ ከተማ ቆመናል፡፡ አዋሽ ሰባት ኪሎ በሚለው
መጠሪያዋ ትታወቃለች፡፡ ከኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር መቆም
ጋር ተያይዞ ደማቋ ከተማ ለዓመታት ፈዝዛ ኖራለች፡፡
አሁን አዋሽ ባቡሩ ጀመረ እንዴ የምታስብል ከተማ
እየሆነች ነው፡፡
መንገድ አንጀምርም፤ ከዚያ በፊት ዳጉ ያስፈልጋል፡፡ ዳጉ
የአፋሮች ቁልፍ እሴት ነው፡፡ አፋር ከዘመን ቀድሞ
የመረጃን ፋይዳ የተገነዘበ ህዝብ ነው፡፡ መረጃን በፍጥነት
የሚለዋወጡበት እሴት ዳጉ ይባላል፡፡ ያለ ዳጉ ህይወት
የለም፡፡ የአፋሮች ዳጉ ፈጣንና እውነተኛ ነው፡፡ ተአማኒነቱ
የተለየ መገለጫው ሲሆን በፍጥነትም ወደር የለውም፡፡
ቡሬሙዳይቱ የተከሰተው ሳይረፍድ ኤሊዳር ይሰማል፡፡
ማንዳ የተከወነው ሳይዘገይ አፍዴራ ይገባል፡፡ ሙሳ አሊ
የተወራው አዘሎ ሲደርስ ደከመኝ ብሎ መንገድ ሳያድር
ነው፡፡ ከበርሐሌ ዱብቲ፣ ከአሳኢታ ሚሌ ዳጉ ፈጥኖ
የሚደርስ የመረጃ መለዋወጫ ስልት ነው፡፡ ፍጥነቱ
የደወሉላቸው ደንበኛ ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ
ናቸው ከሚለው የስልካችን አገልግሎትም የሚፈጥንበት
ጊዜ አለ፡፡
የአፋሮች እንቅስቃሴ በዳጉ የተደገፈ ነው፡፡
ስለሚደርሱበት አካባቢ በቂ መረጃ በየደረሱበት
ይሰማሉ፡፡ ስለአለፉባቸው አካባቢዎች ደግሞ
ለደረሱባቸው ስፍራዎች አስተማማኝ መረጃ ይሰጣሉ፡፡
ይሄ ከማህበራዊ ትስስራቸው ባሻገር የኢትዮጵያን ድንበር
ሳትደፈር ተከብራ እንድትኖር በጽናት እንዲጠብቁ
ያስቻላቸውን ብቃት የፈጠረ እሴት ነው፡፡
አዋሽ ሰባት ቆመን ዳጉ እንሰበስባለን፡፡ ከዚያ ጉዞው
ይቀጥላል፡፡ የአዋሽ አርባን ሙቀት እንጋራዋለን፡፡ በመተካ
ፍል ውሐዎች እንጠበላለን፡፡ የአፋር ምድር አማካይ
የሙቀት መጠን ዝቅ ሲል 18 ከፍ ሲል 45 ዲግሪ
ሴንቲግሬድ ይደርሳል፡፡ እንደ ምድሩ እንለብሳለን፡፡
ጉዞአችን ወደ አፋሮች ምድር ነው፡፡