ይህ ሰው ሁሌም በመረጃ አሰባሰብ በዝግጅት አቀራረቡ
እና በሌሎች ነገሮቹ ድንቅ ከሚሉኝ ሰዎች ውስጥ አንድ
ነው።
ሁለገቡ ሰው ገነነ መኩሪያ( ሊብሮ) ።
ሊብሮ የምትለውን ስያሜ ያወጣለት በአብዛኛው
የእግርኳስ አፍቃሪ በአዝናኝነቱ በእግር ኳስ ወዳድነቱ
የሚታወቀው የኳስ ሜዳው ሰው ሀይሌ ካሴ ነው።
በወቅቱ ጊዮርጊስ ከሜታ አቦ በተጫወቱበት ጊዜ ነው
አምስት ተጫዎችን አልፎ ባስቆጠረበት ጊዜ ነበር
የተቀፅላው መነሻ ።
ሊብሮ የተወለደው ይርጋለም ከተማ ቢሆንም እድገቱ ግን
ሻሸመኔ ቀበሌ 09 ነው ።
በልጅነት ወቅትም እግርኳስ ይወድ የነበረው ገነነ
በጊዜው በየ15 ቀኑ አአ የሚመጡት የሆቴላቸው ሾፌር
አብሮቸው ያቀና ነበር በነበራቸው ቆይታም ካምቦሎጆ
ገብተው እግር ኳስ ተመልክተው ይመጡ ነበር በዛ
በአፋላነት ጊዜው መሆኑ ነው።
ሌላው የሚገርመው ገኔ ሻሸመኔ ውስጥ ላለ ቡድን ለ A
ም፣ለB፣ ለC ይጫወት ነበር በአንድ ቀን ውስጥ ።
የቀበሌ 09 ቡድንም በወቅቱ የአቶ ሙኩሪያ ቀበሌ ቡድን
ይባል ነበር ። በጊዜው እሱን ጨምሮ ስድስት ወንድሞቹ
እዛ ቡድኑ ውስጥ ይጫወቱ ነበሩ።እንደዚህ እያለ ነው
ወደ እግር ኳስ ተጫዎችነት ያመራው። ወደ ክለብ
ደረጃም መጀመሪያ የመጣው በ1975 አመተምህረት
አከባቢ በነበረ የትምህርትቤት ውደድሮች ላይ በመታየት
ከነ ታሪኩ መንጀታ፣አስቻለው ጋር በመሆን ነበር ወደ ሜታ
ቢራ የተቀላቀለው።
እዚህ ጋር በወቅቱ በአጨዋወትና በሌሎች ተዛማጅ
ነገሮች ከዛን ጊዜ ጀምሮ ከአሰልጣኞች ጋራ ሙግት
ይገጥም ነበር ።በጊዜው ሜታን ያሰለጥን ከነበረው ስዮም
ጋር ይጋጩ እንደነበር ይጠቀሳል።
በእግር ኳስ ተጫዎችንነት ወቅት እረፍት ሰአቱን በማንበብ
ማሰለፍ ይወድ እንደነበር አብሮት የተጫወቱት
ይመሰክራሉ ።
የሊብሮ ጋዜጣው መነሻ
ከዛ በፊት በበጎ ፍቃደኝነት በተለያዬ የህትመት እና
የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ይሰራ ነበር። ከሰራባቸው
የህትመት ሚዲያ ውስጥም መረሀ ስፖርት፣ የኢትዮጱያ
ራዲዮና ቴሌቪዥን ውስጥ ይጠቀሳል ።
በመቀጠል ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ማለትምአበበ ወልደ
ፃዲቅ ፣ሁሴን አብድልቀኒ ፣ጋር በመሆን ሻምኘዮን
የምትባል የስፖርት ጋዜጣ መስርተው ሰርተዋል።
በማስከተለም የራሱ የሆነችውን ሊብሮ ጋዜጣ አቋቋመ
።በዚህ አጋጣሚ የዚች ጋዜጣ አመሰራረት የሚገርም ነው
በተለይ በወቅቱ የነበሩቱ የቦሌ ማተሚያ ስራ አስኪያጂ
አሰፋ ከበደ ሊመሰገኑበት የሚገባ ድርጊት ነው ።በጊዜው
ገነነ የሚያሳትምበት ገንዘብ እጥረት ያጋጥመዋል ሁሉ
ነገር ጨርሶ ከሰራ በኋላ ነገር ግን እጅን አጣጥፈ ከሰማይ
መና አልጠበቅ ወደ ቦሌ ማተሚያ ቤት ሄዶ ስራ
አስኪያጅን ያለበትን ነገር ሁሉ አስረድቶ ጠይቆ በእሳቸው
ቀና ትብብር አማካኝነት ለህትመት ለመጀመሪያ ጊዜ በቃች
።በጊዜውም በጣም ተወዳጅ ጋዜጣ እንደነበረች በጊዜው
የነበሩ ሰዎች ያስታውሳሉ አብዛኛዋን ትኩረት
የምታደርገው የሀገር ውስጥ ዜናዎች ላይ ነበር ።ለነገሩ
አብዛኛዎ የዛን ዘመን ጋዜጦች ትኩረታቸው የሀገር ውስጥ
እንደነበር መመልከት ይቻላል።
በህትመት ግን ለ13 አመታት ከብዙ ችግሮች ጋር
እየተጋፈጠች ለህዝብ ተደራሽ መሆን ችላ ነበር ።
አብዛኛውን ስራ እራሱ ገነነ ነበር የሚሰራው ።የጋዜጣ ስራ
ምን ያህል አድጋሚና እርዳታ እንደሚያስፈልገው መሆኑ
የሚያውቀው ያውቀዋል።
ነገር ግን ጋዜጣዋ ከተቋረጠች በኋላ ለአጭር ጊዜ በድረ
ገፁ በኩል ጀምሮት ነበር ። ቢሆንም ግን ሊዘልቅ
አልቻለም ።ለሌሎች የምርመራና መፅሀፍ ለመፆሀፍ ፈልጉ
ሁሉ ነገር ገታ አድርጉ በመተው በመፅሀፋና ሌሎች
ተዛማጅ መስኮች ላይ በመስራት በተከታታይ በእግር ኳስ
ዙራያና ፖለቲካ የሚያጠነጥኑ መፅሀፎችን አበረከተለን
ለመጥቀስ ያክል
የአሸናፊ ግርማ የህይወት ታሪክ ከአሸዋ ሜዳ እስከ
አርጀንቲና
የእግር ኳስ ወጎች
ኢሀፖና ስፖርት 1 ና2 (አዚጋ በቅርብ ለእይታ የቀረበው
የነገን አልወልድም የታሪኩ መነሻ ከ ኢሀፖና ስፖርት 1
የተወሰደ ነው)
እና ሌሎች በህትመት ደረጃ ያልወጡ በሙዚቃና በሌሎች
ጉዳዮች ያተኮሩ መፅሀፍች እያሰናዳል ይገኛል ።
ሌላው በ90 ናዎቹ አጋማሽ ላይ በስፋት ይወራ
ስለነበረው የኢትዮጱያዊ ስልጠና ሀሳብ አመንጪ ሰው
ነው በተለምዶ Gk የሚባለውን የስልጠና ፍልስፍና በዋላ
በካሳዬ አራጌ ዳብሮ ለአጭር ጊዜ የተሞከረው
።በነገራችና ላይ በዚህ ዙሪያ ላይ 1994 ላይ ኢትዮጱያ
ስልጠና መፅሀፋ ማውጣቱ አይዘነጋም ።አስከ ጠቅላይ
ሚኒስተር ደረጃ ደብዳቤ ፅፎል በስልጠናው ዙሪያ ላይ ።
በአሁኑ ወቅት ገኔ በስፋት በብስራት fm ላይ እየሰራ
ይገኛል ።በትውስታ፣ በዘመን ተሻጋሪ ና በመሴ ሪዞርት ላይ
ማለት በተለይ የቀድሞ ጊዜ ትውስታዎች ላይ ያተኮሩ
ዝግጅቶቹ የማይጠገቡ መሆኑ ዝግጅቱን ማድመጥ ብቻ
በቂ ናቸው።በቃ ገነነ ማለት የመረጃ ቋት ነው። እዚጋ
ሀይሌ ካሴ ያላትን ነገር ላካፋላቹ። በተለይ በስልጠናው
ዙሪያ "ገነነ እና ካ ሳዬ ማለት ማሽን ናቸው
ልንጠቀምባቸው ይገባል የሌላ ሀገር ዜጉች ቢሆኑ ግን
እንቀበላቸው ነበር" እያለ በቁጭት ነግሩናል ሀይሌ ካሴ
በመጨረሻም እኛ በዚህ ዘመን ያለን የቀድሞን ጊዜ
ያልተመለከትን ሰዎች እንደአንተ አይነቱ ሰዎች ይብዙልን
ታሪኩን እና እድገቱን ለማወቅ ለሚፈልግ ትውልድ አንተ
አንዱ ተጠቃሽ ነክ ላንተ ክብር ይሆን ዘንድ ይህን
ከሰማሁትና ከማውቀው ስለአንተ ፃፍኩ።
*
*
*
እናመሰግናለን የአስቴር አየለ ባለቤት የናኦድና የኤሉም
አባት ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ)።
# Dagim Tamiru
ረቡዕ 6 ጁላይ 2016
ትንሽ በጥቂቱ ስለ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ )የማውቀውን
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)