ረቡዕ 11 ሜይ 2016

ዛሬ 03/09/08 በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ

ዛሬ 03/09/08 በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ በቀበሌ 16 በሚገኝው በልማድ ፖሊስ ካምፕ በሚባለው ቦታ ለከተማችን ሁለተኛው ስፖርት ማዘውተሪያ ቦታ ሙሉ በሙሉ ወጪው በዳሽን ቢራ አ.ማ የሚገነባው ሜዳ የመሰረት ድንጋይ በከንቲባችን በአቶ ተቀባ በዳሽን ቢራ አ.ማ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ መክብብ እንዲሁም የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች እንግሊዛዊው ማርቲን ሬይሞንድ ኬውን በተገኙበት የተቀመጠ ሲሆን በጎንደር መስቀል አደባባይ በተካሄደው ፐሮገራም ለአገሪቱ እግር ኳስ እድገት መሠረት የሆኑትን የታዳጊ የእግር ኳስ ተጫዋቾችንና አሰልጣኞችን ማበረታታት የጉብኝቱ ዋነኛ ዓላማ ሲሆን ማሪቲን ኬውን በቆይታው በአዲስ አበባና በጎንደር የልማት ስራዎችን ይጎበኛል።ከዳሽን ቢራና ከፋሲል ከነማ እግር ኳስ ተጫዋቾች ጋር ተዋወቃል።
ከፕሮጀክት እግር ኳስ ተጫዋቾች ጋር ጨዋታ ያደረገ ሲሆን ፣ ኳሶችንና ፒፕስ በስጦታ የበረከተ ሲሆን ከሰአት ደግሞ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ለመጎብኝት ሂድዋል ኬውን በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ከሚሰለጥኑ ታዳጊ ወጣቶች ጋርም የእግር ኳስ ጨዋታ ያደርጋል።
እንዲሁም ከአሰልጣኞችና ከሌሎች የስፖርት ባለሙያዎች ጋር የልምድ ልውውጥ ያካሂዳል።
የአርባ ዘጠኝ ዓመቱ ማርቲን ኬውን በአርሰናል፣ በሬዲንግ፣ በኤቨርተን እና በአስቶን ቪላ ክለቦች ተጫውቷል።ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ የሚጣው የእንግሊዙ የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከዳሽን ቢራ አክሲዮን ማህበር በእግር ኳስ ላይ በጋራ ለመስራት ባደረጉት ስምምነት መሠረት ነው። እንዲሁም ለጎንደር ከተማ አስተዳደር ቤት ለተቃጠለባችወ ለችግረኞች ዳሽን ቢራ አ.ማ የ 600000 ብር ድጋፍ ለከንቲባው አበርክተዋል ፡፡ አንተነህ መሀሪ የዳሽን ቢራ ስፖርት ክለብ ህዝብ ግንኙነት

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ