ሐሙስ 15 ፌብሩዋሪ 2018

ሰበር ዜና... ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ስልጣናቸውን ለመልቀቅ ጥያቄ አቀረቡ

አዲስ አበባ የካቲት 8/2010 ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከኢህአዴግ ሊቀመነበርነትና ከአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው ለመልቀቅ ጥያቄ አቀረቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣን ለመልቀቅ ያቀረቡት ጥያቄ በአገሪቱ የተፈጠረው አሳሳቢ ሁኔታ እልባት እንዲያገኝ የመፍትሄው አካል ለመሆን ነው ብለዋል።
ከስልጣን ለመልቀቅ ያቀረቡትን ጥያቄ ድርጅታቸው ደኢህዴን የተቀበለው ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትርነታቸውን ለመልቀቅ ያቀረቡት ጥያቄም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ ታውቋል።


ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ