ረቡዕ 10 ጃንዋሪ 2018

ሶስቴ ለመደገስ አቅም የለኝም ያለው ሰው በአንድ የሰርግ ስነ ሰርዓት ሶስት ሚስቶችን አግብቷል

 ሶስት ሚስቶችን ለማግባት ሲሰናዳ የኖረው ሰው የተለያዩ ሰርጎችን የመደገስ አቅም የለኝም በሚል በአንድ የሰርግ ስነ ስርዓት ሶስት ሚስቶችን አግብቷል። የ50 ዓመት ዕድሜ ያለው ኡጋንዳዊው መሃመድ ሰማንዳ፥ በፈፀመመው ተግባር የአፍሪካን መገናኛ ብዙሃን ቀልብ ስቧል ነው የተባለው። 
ሰማንዳ ሶስቱን ሴቶች ለማግባት ቢፈልግም፥ ለእያንዳንዷ ሴት በተለያዩ ጊዜያት ሰርግ የመደገስ አቅም የለኝም ሲል ተናግሯል።
ሰማንዳ በኡጋንዳ ዋኪሶ ግዛት ነዋሪ ሲሆን፥ ምግብ በመሸጥ የሚተዳደር ነው። የ50 ዓመቱ ሰው ያገባቸው ሶስቱም ሴቶች ምንም ዓይነት ቅናት እንደሌለባቸው የገለፀ ሲሆን፥ ኑሯቸውን ለመደገፍ ጠንክሮ እንደሚሰራ ነው የተናገረው።

ምንጭ፦ (ኤፍ.ቢ.ሲ) www.odditycentral.com

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ