ማክሰኞ 17 ዲሴምበር 2019

#ቦይንግ ከደህንነት ስጋት ጋር በተያያዘ የ737 ማክስ አውሮፕላን ምርትን በጊዜያዊነት ሊያቋርጥ መሆኑን አስታውቋል።

እንደ ኩባንያው ገለፃ የ737 ማክስ አውሮፕላን ምርት ከፊታችን ጥር ወር ጀምሮ በጊዜያዊነት የሚቆም መሆኑ ታውቋል።

የኩባንያው ቦርድ ለሁለት ቀናት በአሜሪካ ቺካጎ ከተወያየ በኋላ ነው የአውሮፕላን ምርቱ እንዲቆም ውሳኔ ያሳለፈው ተብሏል።

ይህ የሆነውም የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር ከአውሮፓውያኑ 2020 በፊት አውሮፕላኖቹ ወደ በረራ እንዲገቡ ፍቃድ አልሰልጥም ማለቱን ተከትሎ ነው።

የቦይንግ ምርት በሆኑት 737 ማክስ አውሮፕላኖች በኢትዮጵያ እና በኢንዶኔዢያ በደረሰ አደጋ በድምሩ የ346 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትትሎ ካሳለፍነው ዓመት መጋቢት ወር ጀምሮ ከአገልግሎት ውጭ ተደርገው መቆማቸው ይታወሳል።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ