ሰኞ 16 ዲሴምበር 2019

#ፎርብስ መፅሔት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ከዓለማችን 100 ተፅእኖ ፈጣሪ ሴቶች አንዷ አድርጎ መረጠ፡፡ ፕሬዝዳንቷ በ2019 የአፍሪካ ብቸኛዋ ተመራጭ ናቸው፡፡


መፅሔቱ ለያዝነው የፈረንጆቹ ዓመት ባወጣው የዓለማችን ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች ዝርዝር ውስጥ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅን በ93ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧቸዋል፡፡
መፅሔቱ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በአፍሪካ ብቸኛዋ በስልጣን ላይ ያሉ ሴት የአገር መሪ እንደሆኑ አስፍሯል፡፡
ፕሬዝዳንቷ ወደዚህ ታላቅ ኃላፊነት በተሾሙ ጊዜ ለህዝብ እንደራሴዎች ባደረጉት ንግግር የሴቶች ድምፅ ለመሆን ቃል መግባታቸውንና የአንድነትን አስፈላጊነት አስረግጠው መናገራቸውን መፅሔቱ አስታውሷል፡፡
የጀርመኗ መራሄተ መንግስት አንጌላ መርክል፣ የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ መሪ ክርስቲያን ላጋርድ እንዲሁም የዩናይትድ ስቴት ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ ከአንድ እስከ ሶስተኛ ደረጃ እንደያዙ መረጃው አመልክቷል፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ