ረቡዕ 14 ማርች 2018

ለሴት ልጃቸው የወንድ ስም የሰጡት ወላጆች ፍርድ ቤት ቀረቡ

ቤተሰቦች ስም ለማውጣት ብዙ ክርክሮች ያደርጋሉ ያለው ሚረር በፈረንሳይ ግን ከዚህ በተለየ ለሴት ልጃቸው የወንድ ስም በማውጣታቸው ፍርድ ቤት መቅረባቸው ተነግሯል።
ለህፃኗ ልጅ ቤተሰቦቿ “ሊያም” የሚል ስም ቢያወጡላትም ፍርድ ቤቱ ለሴት ልጅ የሚሆን ስም አይደለም ብሎ ማገዱ ነው የተነገረው።
 የልጅቱ ስም የህፃናትን ፍላጎት የሚፃረር እና በማህበራዊ ግንኙነት ላይ ትፅዕኖ ሊያሳድር የሚችል በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ስሙን ሊያግደው እንደሚገባ አቃቤ ህጎች ተናግረዋል።
በተጨማሪም ስሙ ፆታዊ የሆኑ ብዠታዎችን ይፈጥራል ተብሏል።
ጉዳዩን የሚከታተለው ፍርድ ቤት የህፃኗ ቤተሰቦች አዲስ ስም እንዲያወጡ ማዘዙም ተገልጿል። 
ሆኖም የህፃኗ ቤተሰቦች ልጃቸው ባውጡላት ስም እንድትጠራ እንደሚፈልጉና ለዚህም የህግ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የተናገሩ ሲሆን፥ የህፃኗን ጥምቀት( baptism) ማራዘማቸው ታውቋል።
በልጃቸው ስም ምክንያት ፍርድ ቤት የቆሙት ወላጆች ጉዳይ ለልጆች ስም ማውጣት ላይ ጥብቅ ስርዓት አላት በምትባለው ፈረንሳይ ያልተለመደ መሆኑ ተነግሯል።
ከዚህ በፊት በፈረንሳይ ኑታላ፣ ስትሮዎበሪ እና ማንሃታ የተሰኙ ስሞች ለልጆች ማውጣት መከልከሉ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ሚረር(ኤፍ.ቢ.ሲ)

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ